የጐንደር ከተማ አስተዳደር በአንድ ነጥብ ሁለት ሚሊየን ብር ሶኒክ ስክሪን አሰርቶ ከትናንት ወዲያ አስመረቀ፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ አታላይ ዓለም ለአዲስ አድማስ እንደገለጹት፤ ግዙፉ ሶኒክ ስክሪን የተሰራው ለከተማ ወጣቶች የመዝናኛ አማራጭ ለመስጠት፣ ባለሀብቶች ምርት እንዲያስተዋውቁበትና ለአጠቃላይ የመረጃ ልውውጥ ነው፡፡
በከተማው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት የሚንቀሳቀሰው ሶኒክ ስክሪን ከ3 መቶ ሺህ በላይ ለሚሆነው የከተማዋ ነዋሪ አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡