በደብረዘይት ከተማ ኪነ - ጥበብ አፍቃሪዎች የተቋቋመውና ላለፉት ዓመታት ወርሃዊ ኪነ - ጥበባዊ ዝግጅቶችን እያቀረበ ያለው "ሆራ ጉላ" የስነጽሑፍ ማህበር "ቃና ጥበብ" የተሰኘ ዝግጅቱን ለመውሊድ በዓል በመጪው ሐሙስ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ በቢሾፍቱ ሁለገብ ሲኒማ አዳራሽ እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ የዕለቱ የክብር እንግዳ እንደምትሆን በምትጠበቀው አንጋፋዋ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል ፊት የማህበሩ አባላትና ሌሎች እንግዶች የግጥም፣ መነባነብና ወግ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡