Saturday, 19 January 2013 14:51

"ቺኮሎጂ" ሳታየር ኮሜዲ ፊልም ይመረቃል

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(0 votes)

በረዳት ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ጃዋሬ የተሰራው "ቺኮሎጂ" የተሰኘ ሳታየር ኮሜዲ ፊልም ነገ በግል ሲኒማ ቤቶች እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡
ጃዋሬ ፕሮዳክሽንስ ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ፤ ፊልሙ በልዩ ጥናት ላይ ተመስርቶ እንደተሰራና ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት አስታውቋል፡፡ ከሰማንያ በላይ ነባርና አዳዲስ ተዋንያን ተሳትፈውበታል የተባለው "ቺኮሎጂ"፤ በቅርቡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በመላው አገሪቱ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በልዩ ስነስርዓት እንደሚመረቅና በሁሉም ሲኒማ ቤቶች በመደበኛ ፕሮግራም እንደሚቀርብ ተገልጿል፡፡

Read 1969 times