Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Tuesday, 01 November 2011 14:08

ዊል ፋረል የክብር ሽልማት ተቀበለ ኤዲ መርፊ ትወና እንደ ሰለቸው ተናገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዊል ፋረል በማርክ ትዌይን የተሰየመ የኮሜዲ አዋርድ እንደተሸለመ ሲኤንኤን ዘገበ፡፡ የክብር ሽልማቱ በፊልም እና ሌሎች ኪነ ጥበባዊ ስራዎቻቸው የአሜሪካን ማህበረሰብ በጥሩ መንገድ ቀርፀዋል ተብለው ለተመረጡ የኮሜዲ ተዋናዮች የሚዘጋጅ ነው፡፡ ኮሜድያኑ ዊል ፋረል ልዩ የክብር ሽልማቱን ባለፈው እሁድ በጆንኤፍ ኬኔዲ ማዕከል በተደረገ ስነስርዓት ላይ ተቀብሏል፡፡ ከ1998 እ.ኤ.አ ጀምሮ ይህን የክብር ሽልማት ካገኙት ታዋቂ የፊልም ጥበብ ባለሙያዎች መካከል ቲና ፌይ፤ ሪቻርድ ፕሬየር፤ ቦብ ኒው ሃርት፤ ሎረኔ ሚካኤልስና ስቲቭ ማርቲን ይገኙበታል፡፡ የሃብት መጠኑ እስከ 80 ሚሊዮን ዶላር የሚገመተው የ44 ዓመቱ ዊል ፋሬል፤ በአንድ ፊልም 20 ሚሊዮን ዶላር ከሚከፈላቸው ጥቂት ተዋናዮች አንዱ ነው፡፡

በሌላ ዜና የ50 ዓመቱ ኤዲ መርፊ፤ የቤተሰብ ፊልሞችን መስራቱን አቁሞ በስታንድ አፕ ኮሜዲ ሊሰራ መወሰኑን “ዘ ሮሊንግ ስቶን” መጽሔት ዘገበ፡፡ ኤዲ መርፊ በሚቀጥለው የፈረንጆች ዓመት የሚደረገውን 84ኛው የኦስካር ሽልማት ስነስርዓት በመድረክ መሪነት እንዲያስተናብር ተሹሟል፡፡ ከ”ሮሊንግስ ስቶን” መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ፊልም የመስራት ጊዜዬ ያበቃ ይመስለኛል ያለው ኤዲ መርፊ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእለት ተእለት ስራው ቤቱ ተቀምጦ ጊታር ሲጫወት መዋል እንደሆነም ተናግሯል፡፡ ኤዲ መርፊ በስታንድ አፕ ኮሜዲ ሲሰራ የነበረው ከ30 ዓመት በፊት ነበር፡፡በሙሉ ስሙ ኤድዋርድ ሬጋን መርፊ ተብሎ የሚጠራው ይህ ዝነኛ ተዋናይ፤ በፊልም ስራ ከ34 ዓመት በላይ ያገለገለ ሲሆን በፊልም ደራሲነት፣ ዲያሬክተርነትና በድምፃዊነትም ሰርቷል፡፡

 

Read 2717 times Last modified on Tuesday, 01 November 2011 14:10