Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Tuesday, 01 November 2011 14:00

ታዳጊዎች የደራሲ ሐዲስን ልደት በትዕይንተ ጥበባት ያከብራሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአዲስ አበባ የሚገኙ ታዳጊዎች እና ሕፃናት የክቡር ዶክተር ሐዲስ አለማየሁን ልደት በትዕይንት ጥበባት ያከብራሉ፡፡ ዛሬ ጠዋት በሐገር ፍቅር ትያትር ቤት ትልቁ አዳራሽ በሚቀርበው ዝግጅት የአንጋፋው ደራሲ እና ዲፕሎማት ክቡር ዶ/ር ሐዲስ አለማየሁ 102ኛ ዓመት ልደት መታሰቢያ ይከበራል፡፡ዛጎል ቤተመፃሕፍት ባዘጋጀው ዝግጅት “ተረት ተረት የመሠረት” ከሚለው የደራሲው መፅሐፍ ድራማዊ ትረካ፣ የልጆች ግጥም፣ ሥእል፣ ዳንስ፣ ሙዚቃና መሠል ዝግጅት ይኖራል፡፡ የክብር ዶክተር ሃዲስ አለማየሁ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና የወ/ሮ ክበበፀሃይ (ባለቤታቸው) ሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅት ሠራተኞች የክብር እንግዳ በሚሆኑበት ዝግጅት የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው በለጠ፤ ሐዲስ አለማየሁ በደራሲነትና በዲፕሎማትነት ስላደረጉት አስተዋፅኦ ገለፃ ያደርጋሉ፡፡ በዝግጅቱ ከአዲስ አበባ ከተውጣጡ ታዳጊ ወጣቶች ሌላ ገጣሚ ሜሮን ጌትነት፣ ድምፃዊት ሙኒት መስፍን፣ እና ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Read 4286 times