በሌላም በኩል ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህር ቤቶች ለተመረጡ አንድ መቶ ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ማሻሻያ ኮርስ ሊሰጥ ነው፡፡ ከአሜሪካ ኤምባሲ በተገኘ 38 ሺህ ዶላር የተጀመረው ኮርስ ከደጃች ባልቻ፣ ሸመልስ ሃብቴ፣ ጥቁር አንበሳ እና አፍሪካ ሕብረት ሁለተኛ ደረጃ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች የሚሰጠው ኮርስ ለሁለት ዓመታት ይቀጥላል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ አርት ሀበሻይ የኪነጥበበ የመረጃና መዝናኛ ማዕከል ለሁለት ወራት በፊልም እና ትያትር ያሰለጠናቸዉን ሰልጣኞች ነገ ከጧቱ 3 ሰዓት ያስመርቃል፡፡ በሀገር ፍቅር ትያትር ቤት የሚመረቁት ሠልጣኞች የፊልምና የትያትር ሥራዎቻቸውን ለታዳሚ ያቀርባሉ፡፡