Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 15 October 2011 12:13

“ሰባ ሰላሳ” ፊልም ነገ፤ |እናት የግጥም ጓዳ´ ዛሬ ይመረቃሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

|904´ የሚደመጥ ኮሜዲ ገበያ ላይ ዋለ
አማኑዔል መሀሪ ጽፎት ቢኒያም ወርቁ ያዘጋጀው “ሰባ ሰላሳ” የአማርኛ ፊልም ነገ በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች ይመረቃል፡፡ ፊልሙን የሰራው አስቴር ፊልም ፕሮዳክሽን እንደገለፀው፤ የአዲስ አበባው ዋነኛ ምርቃት ከቀኑ 8 ሰአት በአምባሳደር ሲኒማ ይከናወናል፡፡ በዘጠና ደቂቃ ፊልሙ ላይ ደበበ እሸቱ፣ የሻሽወርቅ በየነ፣ ፍቃዱ ከበደ፣ ይገረም ደጀኔ፣ ዳግማዊት ፀሐዬ፣ ሰሎሞን ቦጋለና ሌሎችም ተውነዋል፡፡ በሌላም በኩል የአቶ አብርሃም መለሰ “እናት የግጥም ጓዳ” የግጥም መፅሐፍ ዛሬ ጧት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ይመረቃል፡፡ 113 ገፆች ያሉት መፅሐፍ 30 ብር ይሸጣል፡፡ይህ በእዚህ እንዳለ “904” አዲስ የኮሜዲ የሚደመጥ (audio) ሲዲ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ የሲዲው አቅራቢ ቴዎድሮስ ታለ (ኩኩሻ) ነው፡፡ ኩኩሻ ካሁን ቀደም ለኮሜድያን ስክሪፕት በመፃፍ ይታወቃል፡፡ በድምፅ ብቻ በሚደመጥ ኮሜዲ ማሳቅ ከባድ ነው ያለው ኮሜዲያኑ፤ ተስፋዬ ካሳ ግን የተዋጣላት እንደነበር ተናግሯል፡፡

Read 3629 times