ዩሲኤልኤ ፊልምና ቴሌቭዥን ድርጅት ለ2 ወራት የሚዘልቅና አዲስ የሲኒማ ጥበብ የፈጠሩ ጥቁር የፊልም ባለሙያዎችን የሚዘክርበት ፌስቲቫል ያዘጋጀ ሲሆን፤ በ1979 እ.ኤ.አ “ቡሽ ማማ” እና “አሽስ ኤንድ ኤምበርስ” በሚል የተሰሩት የኃይሌ ገሪማ ፊልሞች በፌስቲቫሉ እንደሚካተቱ ታውቋል፡፡ በሌላ በኩል በ400 ሚሊዮን ዶላር በጀት ሎስአንጀለስ ውስጥ የሆሊውድ ሙዚዬም ሊገነባ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት የግንባታ ስራው የሚጀመረው ሙዚየሙ፤ ግንባታው ሲጠናቀቅ 42 ሚሊዮን የፊልም ፖስተሮችና ከ10 ሚሊዮን በላይ የፊልም ፎቶግራፎች እንደሚቀመጥበት ተግናሯል፡፡