በፊልም ጥበብ ዙርያ ላለፉት አምስት አመታት ባለሙያዎችን ልምድ ሲያቀሳስም የቆየው አላቲኖስ የፊልም ሰሪዎች ማህበር፤ “የተዋናይ ግሩም ኤርምያስ የአተዋወን ብልሃት” የሚል የጥናት ወረቀት ሊያቀርብ ነው፡፡ የጥናት ወረቀቱ የሚቀርበው በሩስያ የሳይንስና የባህል ማእከል ፑሽኪን አዳራሽ በመጪው ሐሙስ ከቀኑ 11 ሰዓት ነው፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ አንጋፋው የኢትዮጵያ የፊልም ባለሙያ ሚሼል ፓፓታኪስ ከትናንት ወዲያ ምሽት በፑሽኪን አዳራሽ ልምዳቸውን አጋርተዋል፡፡