Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 24 September 2011 10:42

የታላቁ ሩጫ ውድድር በተሳካ ሁኔታ ተጀመረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ታላቁ ሩጫ ከኮካ ኮላ በመተባበር ያዘጋጀው  የ7 ኪ.ሜ ተከታታይ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ከሳምንት በፊት በተሳካ ሁኔታ መጀመሩን አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡ በኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ውድድሮች በታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ለሰአት መቆጣጣርያ የሚሆን ቺፕ በተገጠመላቸው የመሮጫ ጫማዎች ውድድሩ ተካሂዷል፡፡ 1ኛው የኮካኮላ ሲሬዬስ የ7 ኪሎሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ከሳምንት በፊት ሲካሄድ 3ሺ ተወዳዳሪዎች ተሳትፈው በወንዶች ምድብ መወሰነት ገረመው በ21 ደቂቃ 46 ሴኮንዶች እንዲሁም በሴቶች ምድብ እቴነሽ ድሪባ በ25 ደቂቃ ከ52 ሴኮንዶች ርቀቱን በመሸፈን አሸናፊ ሆነዋል፡፡

በውድድሩ ላይ የሰአት መቆጣጣርያ ቺፕ በተገጠመላቸው ጫማዎች ሁሉም አትሌቶች በመወዳደራቸው ተሳታፊዎች ርቀቱን የሚጨርሱበትን ጊዜ ለማወቅ ከፍተኛ እገዛ አድርጓል ያሉት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጆች የተሳታፊዎች ደረጃና የገቡበት ሰአት ውድደሩ ከተገባደደ በኋላ በሁለት ሰአት ግዜ ውስጥ በድረገፃቸው ይፋ ማድረግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የኮካኮላ የ7 ኪሎሜ ተከታታይ ሩጫ ውድድርን ያዘጋጀው ጤናማ አኗኗርን ለማስፋፋት ባነገበው መርህ ነው፡፡ ቀጣይ ውድድሮች ከ3 ሳምንትና ከ2 ወራት በኋላ እንደሚቀጥሉም ታውቋል፡፡ በውድድሩ በአጠቃላይ 200ሺ ብር ለሽልማት የተዘጋጀ ሲሆን በ3ቱ የኮካኮላ ሲሬዬስ ውድደሮች በመሳተፍ በሁለቱም ፆታዎች ለሚያሸንፉ አትሌቶች ለእያንዳንዳቸው 50ሺ ብር እንደሚበረከት ታውቋል፡፡

 

Read 3285 times Last modified on Saturday, 24 September 2011 10:46