Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 24 September 2011 10:16

መስቀልን የሚዘክሩ ዝግጅቶች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዛሬና ነገ ይቀርባሉ  
የደንጌሳት ምሽት ሐሙስ ቀረበ  
የጉራጌ ብሔረሰብን ባህላዊ የመስቀል አከባበር የሚዘክሩ ዝግጅቶች በእምድብር ከተማ እና በአዲስ አበባ ዛሬ እና ነገ ይቀርባሉ፡፡ ..ጉራጌ ልማ.. በእምድብር ከተማ ዛሬ ከጧቱ 3ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት በሚዘልቅ ዝግጅት የጉራጌ መስቀል አከባበርን ሞዴል በአንድ ቀን ማሳየት የሚል ዓላማ ያለው ሲሆን የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በመስቀል በዓል ልዩ ዝግጅት የሁለት ሰዓት ተኩል የአየር ሽፋን እንደሚሰጠው የጉራጌ ልማት ሕፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ ፈቃደ ተክለማርያም ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀዋል፡፡ እንደ እሳቸው ገለፃ ዝግጅቱ ከመዝናኛነቱ ባሻገር የጉራጌ ሕዝብ ተደራጅቶ የማልማት ሰፊ ልምዱን ለመላው ኢትዮጵያ ያሳይበታል፡፡

በዝግጅቱ ከጉራጊኛ ታዋቂ ድምፃውያን እነ ፀጋዬ ሥሜ እና መውደድ ክብሩ ያቀነቅናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ..የሳምንቱን መስቀል በዓል በአንድ ቀን.. የሚል ዝግጅት በዮድ አቢሲኒያ፣ ባህላዊ ምግብ ቤትና በጉራጌ ባህል ማእከል ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን ነገ ከቀኑ 6 ሰዓት ጀምሮ ቦሌ በሚገኘው ዮድ አቢሲኒያ ምግብ ቤት በአውደርእይ ታጅቦ ይካሄዳል፡፡ በዚህ ዝግጅት ድምፃውያን ሃይሉ ፈረጃ፣ መውደድ ክብሩ፣ ምናሉሽ ረታ፣ ሚሊየን ማሃመድና ሌሎች ተገኝተው ያቀነቅናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወ/ሪት ሊዲያ ፍቅሬ ገልፃልናለች፡፡  
በሌላም በኩል የደንጌሳት ምሽት ሐሙስ ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 6 ሰዓት በቬልቬት የምግብ አዳራሽ ፣ ማክዳ የባህል አዳራሽ ቀረበ፡፡ የጉራጌን ሕዝብ ታሪክና ባህል ጠብቆ በቀረበው ዝግጅት ታዋቂ ድምፃውያን ሥራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን የባህል ዝግጅቱ በምግብና መጠጥ ፌስቲቫልና በችቦ ማብራት ታጅቧል፡፡ በዝግጅቱ ካቀነቀኑ ድምፃውያን መካከል ፀጋዬ ስሜ፣ ምናሉሽ ረታ፣ እና ፈቀለ ማሩ ይገኙበታል፡፡

 

Read 4035 times Last modified on Saturday, 24 September 2011 10:17