ታዋቂው ብሉምበርግ መጽሄት የ2019 የአለማችን አገራት የጤናማነት ደረጃን ዝርዝር ከሰሞኑ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ ስፔን የአንደኛነቱን ደረጃ ከጣሊያን በመረከብ በቀዳሚነት መቀመጧ ታውቋል፡፡
በአለማችን 169 አገራት ውስጥ ለአጠቃላይ የዜጎች ጤናማነት መሰረት የሆኑ ጉዳዮችን ይዞታ በመገምገም የአገራቱን የጤናማነት ደረጃ ይፋ ያደረገው ብሉምበርግ፣ ጣሊያንን በሁለተኛነት አይስላንድን በሶስተኛነት ደረጃ ላይ አስቀምጧቸዋል። ጃፓን አራተኛ፣ ስዊዘርላንድ አምስተኛ፣ ስዊድን ስድስተኛ፣ አውስትራሊያ ሰባተኛ፣ ሲንጋፖር ስምንተኛ፣ ኖርዌይ ዘጠነኛ፣ እስራኤል አስረኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡
እጅግ አነስተኛ የጤናማነት ደረጃ ያላቸው ተብለው ከተዘረዘሩት 30 አገራት መካከል 27ቱ በአፍሪካና በመካከለኛው ምስራቅ ውስጥ እንደሚገኙ የጠቆመው ብሉምበርግ፣ የአገራቱን የጤናማነት ይዞታ ከገመገመባቸው መስፈርቶች መካከል የጤና አገልግሎቶች መስፋፋትና ጥራት፣ የንጹህ ውሃ አቅርቦት፣ ንጽህና፣ አማካይ እድሜ፣ የሲጋራና የአደንዛዥ ዕጾች ተጠቃሚነት፣ ከፍተኛ የሰውነት ክብደት ይገኙበታል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ