Sunday, 17 February 2019 00:00

የተዘረፉ 620 ሚሊዮን የድረገጽ አካውንቶች ለሽያጭ ቀርበዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


          የተደራጁ የኢንተርኔት ዘራፊዎች በህገወጥ መንገድ የሰረቋቸውን 620 ሚሊዮን ያህል የተለያዩ ድረገጾች  አካውንቶች ለሽያጭ ማቅረባቸውን ፎርብስ ዘግቧል፡፡
የኢንተርኔት ዘራፊዎቹ የ16 ድረገጾችን ማለፊያ ቃል ሰብረው በመግባት 620 ሚሊዮን ያህል የተጠቃሚዎችን አካውንቶች በመዝረፍ የኢሜይል አድራሻዎችን የይለፍ ቃልና ሌሎች የግል መረጃዎች በእጃቸው ማስገባታቸውንና ለሽያጭ ማቅረባቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ አካውንቶቹን የሚገዙ ወንጀለኞች ላልተገባ ድርጊት ሊጠቀሙባቸው እንደሚችሉ ስጋት መኖሩን አመልክቷል፡፡
ባለፈው ጥር ወር ላይ 1 ቢሊዮን ያህል የኢሜይል አድራሻዎችና የይለፍ ቃሎች በኢንተርኔት መንታፊዎች መዘረፋቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ በቀናት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በ2.2 ቢሊዮን አካውንቶች ላይ ተመሳሳይ ዝርፊያ መፈጸሙንም አስታውሷል፡፡

Read 2919 times