Saturday, 24 January 2015 13:27

ሞኝ እንደነገሩት

Written by 
Rate this item
(5 votes)

ሞኝ እንደነገሩት
“ፍቅር ያሸንፋል” ስትለኝ አምኜህ
በጦርነት ሁሉ ልሰለፍ አብሬህ
ደብተሬን ቀድጄ
አድርቄ ወጥሬ ጋሻ ሰርቼበት
ብዕሬን ፈልፍዬ ጦር አስቀርጬበት
ጠላትን ወግቼ
ለፍቅር ደምቼ…
ካቀረቀርኩበት ቀና ብል የለህም
ያሸንፋል ባልከኝ አንተ አልተሸነፍክም
እኔ ነኝ ብቻዬን ፍልሚያውን አውጄ
ጦሬን አበጅቼ
እኔው ተማርኬ ራሴን የሰጠሁ
ሙሉው ጦርነቴን
ሙሉ መሸነፌን
ሙሉ መሰጠቴን
ያንተ ድርሻ ቢኖር ልቤን የሰወረው
“ፍቅር ያሸንፋል” ማለትህ ብቻ ነው፡፡
    (ከብሩክታዊት ጐሳዬ “ፆመኛ ፍቅር”
    የተሰኘ የግጥም መድበል የተወሰደ)

Read 3466 times