Saturday, 01 June 2013 14:00

ቢል ክሊንተን በንግግር አቅራቢነት 106 ሚ.ዶ አግኝተዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ቢል ክሊንተን ከዋይት ሃውስ ከወጡ ወዲህ ባለፉት 12 አመታት በተለያዩ ቦታዎች ንግግር በማቅረብ ብቻ 106 ሚሊዮን ዶላር ማግኘታቸው ሲኤንኤን ዘገበ፡፡ ቢል ክሊንተን በአንድ መድረክ ንግግር ለማቅረብ በአማካይ 200ሺ ዶላር ይከፈላቸዋል፡፡ የቀድሞው ፕሬዝዳንት በንግግር አዋቂነታቸው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ተፈላጊ ናቸው፡፡ በናይጄርያ ሌጎስ በአንድ መድረክ የተከፈላቸው 700ሺ ዶላር በተመሳሳይ የስራ ድርሻ የተገኘ ትልቁ ክፍያ እንደሆነ ታውቋል፡፡

ቢል ክሊንተን በንግግር አዋቂነታቸው አምና ከፍተኛ ተፈላጊነት እንደነበራቸው የሚገልፀው ሲኤንኤን በመላው ዓለም በ73 መድረኮች በመስራት 17 ሚሊዮን ዶላር እንደተከፈላቸው ገልጿል። ቢሊ ክሊንተን 42ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የነበሩ ናቸው፡፡ በበጎ አድራጊነት፤ በንግግር አዋቂነት ፤ በዴሞክራት ፖለቲከኛነት እና በጥብቅና ሙያቸው ከፕሬዝዳንትነት ከወረዱ በኋላ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው ቢል ክሊንተን 80 ሚሊዮን ዶላር ሃብት እንዳላቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1609 times