Monday, 27 May 2013 15:11

“ሆሊሲቲ ሲኒማ” ሥራ ይጀምራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በቦሌ አካባቢ ጌቱ ኮሜርሻል ሴንተር ሕንፃ ላይ የተቋቋመው “ሆሊሲቲ ሲኒማ” ነገ ሥራ እንደሚጀምር የሲኒማ ቤቱ ባለቤት አቶ ኃይለማርያም ኪሮስ አስታወቁ፡፡ ነገ ከቀኑ 8 ሰዓት ሥራ አማርኛ ፊልም በማሳየት ሥራ የሚጀምረው ሲኒማ ቤት፣ በሕንፃው ስድስተኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ ሲሆን 250 መቀመጫዎች ያሉት አዳራሽና ካፍቴሪያ አሉት፡፡ የሀገር ውስጥ ፊልም ማሳየቱን በመቀጠልም ከሰኞ እስከ አርብ በቀን ሁለት ፊልሞች፣ ቅዳሜና እሁድ ደግሞ በቀን ሦስት ፊልሞች እንደሚያሳይ ከባለቤቱ መግለጫ መረዳት ተችሏል። ሲኒማ ቤቱ በኮምፒዩተር በታገዘ የትኬት ሽያጭ በመጠቀም ወረፋን ያስቀረ ሲሆን የአካል ጉዳተኞችን ምቾት ታሳቢ በማድረግ እንደተሰራም ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 2278 times