Saturday, 18 May 2013 12:52

ቪን ዲዝል ከፌስቡክ አንድ ቢሊዮን ዶላር ይፈልጋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በ“ፋስት ኤንድ ፊርዬስ” ተከታታይ ፊልሞች ዓለም አቀፍ ዝናን ያተረፈው ተዋናይ ቪን ዲዝል፤ የፌስቡክ ድረገፅን ተወዳጅ በማድረጌ ኩባንያው አንድ ቢሊዮን ዶላር ሊከፍለኝ ይገባል አለ፡፡ በፌስ ቡክ ድረገፅ 48 ሚሊዮን ወዳጆችን ያፈራው ተዋናዩ፤ የፌስቡክን ተወዳጅነት በመጨመር የሚስተካከለኝ የለም ሲል ለ“ኢንተርቴይመንት ዊክሊ” ተናግሯል፡፡ ከአራት ዓመት በፊት የፌስቡክ ድረገፁን እንደከፈተ አንድ ሚሊዮን የሚደርሱ ወዳጆችን በማፍራት ሊፎካከሩት የቻሉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ብቻ እንደነበሩ ያስታወሰው ቪን ዲዝል፤ ከአድናቂዎቹ ጋር በማህበራዊ ድረገፀ መነጋገር በመጀመሩ በተወዳጅነት በዓለም አንደኛ የፌስ ቡክ አድራሻ ይዞ መቆየቱን አብራርቷል፡፡ ተዋናዩ ባለፉት አራት ዓመታት በፌስቡክ ገፁ ከ11 በላይ የፎቶ አልበሞች እና 40 የቪድዮ ምስሎችን በማጋራት ወዳጆቹን ሲያስደስት ቆይቷል፡፡ በአክሽን ፊልሞቹ የሚታወቀው ቪን ዲዝል፤ በ19 ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት፤ በረዳት ተዋናይነት፤ በአዘጋጅነት እና በተባባሪ አዘጋጅነት የሰራ ሲሆን በአጠቃላይ 2.8 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አስገኝቷል፡፡

Read 2482 times