Saturday, 18 May 2013 12:50

“ለቅሶ” ሥእል አውደርእይ ዛሬ ይቀርባል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኢትዮጵያ ብሔረሰቦች የሐዘን ሥርአት ላይ ያተኮረ የሥዕል አውደርእይ ዛሬ እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ የሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የሚቀርበውን የአንድ ቀን የኢንስታሌሽን ሥእሎች የሚቀርቡበት አውደርእይ ያዘጋጁት ትምህርት ቤቱ እና ኑሮዋን ኖርዌይ ባደረገችው ኢትዮጵያዊት ሠዐሊ ማህሌት ኦግቤ ሀብቴ ከሌሎች ሠዐሊያን ጋር በመተባበር ነው፡፡ ዝግጅቱ በዳንስ እና ሌሎች ኪነጥበባዊ ግብአቶች ታጅቦ ዛሬ ከቀኑ 11 ሰዓት እንደሚቀርብ የዝግጅቱ ፕሮዳክሽን ማናጀር መሠረት ኃይሌ በተለይ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡

Read 2393 times