አስራኤል እንድትሄድ ከተወሰነ በኋላ የእስራኤል ዓለም አቀፍ ልማት ትብብር መስርያ ቤት፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የአሜሪካ ይሁዳውያን የጋራ ኮሚቴ እና የሀገሪቱን እጅግ ምርጥ ዶክተሮች ቀዶ ሕክምናውን በነፃ ለማከናወን ቃል ገብተዋል፡፡ ከዶክተሮቹ ውስጥ ውስብስቡን ቀዶ ህክምና ለማድረግ የጠየቁ እጅግ ምርጥ የእስራኤል ዶክተሮች አሉበት፡፡
ከእህቷ ጋር ወደ እስራኤሉ ማዕከል የተጓዘችው የምስራች ከጥልቅ ምርመራ በኋላ የተሳካ የዐይን ፕላስቲክ ቀዶ ሕክምና በዶ/ር ጋይ ቤን ስምኦን እና ዶ/ር ናሆም ሮዘን ተደርጐላታል፡፡ በጥቂት ቀናትም ውስጥ ወደ ወደብ ከተማዋ ሃይፋ በመጓዝ ዶ/ር ዮቭ ቫርዲዘር የፕሮስቴቲክ አይን ከተገጠመላት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ትመለሳለች ብሏል መግለጫው፡፡“ይሄ የተለመደ ቀዶ ሕክምና ስላልሆነ በአንድ ሰው ብቻ አይከናወንም” ያሉት ዶ/ር ቤን ስምኦን በዓለም ዙርያ ካሉ ሌሎች ባለሙያዎች ጋር እንደተወያዩበት ተናግረዋል፡፡ ኪንታሮቱ በትንሽ ቦታ የወጣ ቢሆንም ለዐይነ ሥውርነት የመዳረግና ህይወት የማጥፋት አቅም እንደነበረው ማወቅ ተችሏል፡፡“ዐይን ከፅዮን” በኢትዮጵያ፣ በቪትናም፣ ማይኒማር፣ አዘርባጃን እና ሌሎች ሀገሮች ይሰራል፡፡
በሌላም በኩል ውዴ ፕሮሞሽን እና ኢቨንት ኦርጋናይዚንግ ሃላፊነቱ የተወሠነ የግል ማህበር መጪው ረቡዕ ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ በሚያካሄደው ሦስተኛው የጤና ምሽት ስለ ኦቲዝም እንደሚወያይ አስታወቀ፡፡ በቦሌ ሮክ በተዘጋጀው የጤና ምሽት የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአዕምሮ ሕክምና ክፍል ኃላፊ ዶር. ዮናስ ባህረጥበብ እንዲሁም ሌሎች የህጻናትና ወጣቶች አዕምሮ ሕክምና ባለሙያዎች በምሽቱ ሙያዊ ማብራርያ ይሰጣሉ፡፡ በኢትዮጵያ የኦቲዝም ታማሚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡